1
የማርቆስ ወንጌል 13:13
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
በሁሉም ዘንድ ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
Σύγκριση
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:13
2
የማርቆስ ወንጌል 13:33
ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:33
3
የማርቆስ ወንጌል 13:11
ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፤ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:11
4
የማርቆስ ወንጌል 13:31
ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን አያልፍም።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:31
5
የማርቆስ ወንጌል 13:32
“ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:32
6
የማርቆስ ወንጌል 13:7
ጦርንም የጦርንም ወሬ በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፤ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:7
7
የማርቆስ ወንጌል 13:35-37
እንግዲህ በማታ ቢሆን ወይም በእኩለ ሌሊት ወይም ዶሮ ሲጮኽ ወይም በማለዳ ቢሆን ባለቤቱ መቼ እንዲመጣ አታውቁምና ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ። ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።”
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:35-37
8
የማርቆስ ወንጌል 13:8
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ በልዩ ልዩ ስፍራ የምድር መናወጥ ይሆናል፤ ራብ ይሆናል፤ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:8
9
የማርቆስ ወንጌል 13:10
አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:10
10
የማርቆስ ወንጌል 13:6
ብዙዎች ‘እኔ ነኝ፤’ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:6
11
የማርቆስ ወንጌል 13:9
“እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፤ በምኵራብም ትገረፋላችሁ፤ ምስክርም ይሆንባቸው ዘንድ ስለ እኔ በገዥዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:9
12
የማርቆስ ወንጌል 13:22
ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፤ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ ያስቱ ዘንድ ምልክትና ድንቅ ያደርጋሉ።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:22
13
የማርቆስ ወንጌል 13:24-25
“በነዚያ ቀኖች ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፤ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፤ የሰማያትም ኀይላት ይናወጣሉ።
Διαβάστε የማርቆስ ወንጌል 13:24-25
Αρχική
Αγία Γραφή
Σχέδια
Βίντεο