1
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:23-24
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
በዚህም ልዩነት የለም፤ ሁሉም ፈጽመው በድለዋልና፤ እግዚአብሔርን ማክበርንም ትተዋልና። ጽድቅ ግን በኢየሱስ ክርስቶስም ቤዛነት ያለ ዋጋ በእርሱ ቸርነት ሆነ።
Муқоиса
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:23-24 омӯзед
2
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:22
የሚያምኑበት ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን በእግዚአብሔር ዘንድ ይጸድቃሉ።
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:22 омӯзед
3
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:25-26
እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ፥ በደሙም የሆነ ማስተስረያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም ከጥንት ጀምሮ በበደሉት ላይ ጽድቁን ይገልጥ ዘንድ ነው። እግዚአብሔር ታጋሽ በመሆኑ፥ እሺ በማለቱም እርሱ ጻድቅ እንደ ሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስም የሚያምኑትን እንደሚያጸድቃቸው ዛሬ ያውቁ ዘንድ ነው።
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:25-26 омӯзед
4
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:20
ከኦሪት የተነሣ ኀጢአት ስለ ታወቀች ሰው ሁሉ የኦሪትን ሥርዐት በመፈጸም በእግዚአብሔር ፊት አይጸድቅም።
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:20 омӯзед
5
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:10-12
መጽሐፍ እንዲህ እንዳለ “አንድ ስንኳ ጻድቅ የለም። አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚሻው የለም። ሁሉም ተባብሮ በደለ፤ በጎ ሥራንም የሚሠራ የለም፤ አንድ ስንኳ ቢሆን የለም።
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:10-12 омӯзед
6
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:28
ሰው የኦሪትን ሥራ ሳይሠራ በእምነት እንዲጸድቅ እናውቃለንና።
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:28 омӯзед
7
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:4
መጽሐፍ፥ “በነገርህ ትጸድቅ ዘንድ፥ በፍርድህም ታሸንፍ ዘንድ” ብሎ እንደ ተናገረ እግዚአብሔር እውነተና ነውና፥ ሰውም ሁሉ ሐሰተና ነውና።
ወደ ሮሜ ሰዎች 3:4 омӯзед
Асосӣ
Китоби Муқаддас
Нақшаҳо
Видео