1
ወደ ሮም ሰዎች 8:28
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
እግዚአብሔርን ለሚወዱና እንደ ፈቃዱም ለተጠሩት ሰዎች እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ለበጎ እንደሚያደርግላቸው እናውቃለን።
සසඳන්න
ወደ ሮም ሰዎች 8:28 ගවේෂණය කරන්න
2
ወደ ሮም ሰዎች 8:38-39
ስለዚህ ሞትም ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ባለሥልጣኖችም ቢሆኑ፥ አሁን ያለውም ቢሆን፥ በኋላ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኀይሎችም ቢሆኑ፥ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ማንኛውም ፍጥረት ቢሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ካገኘነው ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ እርግጠኛ ነኝ።
ወደ ሮም ሰዎች 8:38-39 ගවේෂණය කරන්න
3
ወደ ሮም ሰዎች 8:26
እንዲሁም እንዴት መጸለይ እንደሚገባን ስለማናውቅ መንፈስ ቅዱስ በድካማችን ይረዳናል፤ በቃል ሊገለጥ በማይቻል መቃተት ያማልደናል።
ወደ ሮም ሰዎች 8:26 ගවේෂණය කරන්න
4
ወደ ሮም ሰዎች 8:31
እንግዲህ ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን ሊቃወመን ይችላል?
ወደ ሮም ሰዎች 8:31 ගවේෂණය කරන්න
5
ወደ ሮም ሰዎች 8:1
ስለዚህ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚኖሩ አሁን ኲነኔ የለባቸውም።
ወደ ሮም ሰዎች 8:1 ගවේෂණය කරන්න
6
ወደ ሮም ሰዎች 8:6
ሥጋዊ ነገርን ማሰብ ሞትን ያመጣል፤ መንፈሳዊ ነገርን ማሰብ ግን ሕይወትንና ሰላምን ይሰጣል።
ወደ ሮም ሰዎች 8:6 ගවේෂණය කරන්න
7
ወደ ሮም ሰዎች 8:37
እንግዲህ በወደደን በክርስቶስ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ድል በመንሣት ከአሸናፊዎች እንበልጣለን።
ወደ ሮም ሰዎች 8:37 ගවේෂණය කරන්න
8
ወደ ሮም ሰዎች 8:18
የአሁኑ ጊዜ መከራ ወደፊት ለእኛ ከሚገለጥልን ክብር ጋር ቢመዛዘን በምንም ሊተካከል እንደማይችል አድርጌ እቈጥረዋለሁ።
ወደ ሮም ሰዎች 8:18 ගවේෂණය කරන්න
9
ወደ ሮም ሰዎች 8:35
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል ማነው? ችግር ወይስ መከራ? ስደት፥ ወይስ ራብ? ወይስ ራቊትነት፥ ወይስ አደጋ? ወይስ ሰይፍ?
ወደ ሮም ሰዎች 8:35 ගවේෂණය කරන්න
10
ወደ ሮም ሰዎች 8:27
የሰውን ልብ የሚመረምር አምላክ የመንፈስ ቅዱስ ሐሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል፤ መንፈስ ቅዱስ ስለ ምእመናን የሚያማልደው እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነው።
ወደ ሮም ሰዎች 8:27 ගවේෂණය කරන්න
11
ወደ ሮም ሰዎች 8:14
በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው።
ወደ ሮም ሰዎች 8:14 ගවේෂණය කරන්න
12
ወደ ሮም ሰዎች 8:5
በሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ ሥጋዊ ነገርን፥ በመንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን መንፈሳዊ ነገርን ያስባሉ።
ወደ ሮም ሰዎች 8:5 ගවේෂණය කරන්න
13
ወደ ሮም ሰዎች 8:32
እግዚአብሔር ለአንድ ልጁ ሳይራራ ስለ እኛ አሳልፎ ከሰጠው እንዴት ከልጁ ጋር ሁሉን ነገር በነጻ አይሰጠንም?
ወደ ሮም ሰዎች 8:32 ගවේෂණය කරන්න
14
ወደ ሮም ሰዎች 8:16-17
የእግዚአብሔር መንፈስ ከእኛ መንፈስ ጋር ሆኖ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ለእኛ ይመሰክራል። እንግዲህ የእግዚአብሔር ልጆች ከሆንን የእርሱ ወራሾች ነን፤ ከክርስቶስም ጋር እንወርሳለን፤ አሁን የክርስቶስ መከራ ተካፋዮች ብንሆን በኋላ የክብሩ ተካፋዮች እንሆናለን።
ወደ ሮም ሰዎች 8:16-17 ගවේෂණය කරන්න
15
ወደ ሮም ሰዎች 8:7
ሥጋዊ ነገርን የሚያስብ ሰው ለእግዚአብሔር ሕግ ስለማይታዘዝና መታዘዝም ስለማይችል የእግዚአብሔር ጠላት ነው።
ወደ ሮም ሰዎች 8:7 ගවේෂණය කරන්න
16
ወደ ሮም ሰዎች 8:19
ፍጥረት ሁሉ የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ በታላቅ ናፍቆት ይጠባበቃል።
ወደ ሮም ሰዎች 8:19 ගවේෂණය කරන්න
17
ወደ ሮም ሰዎች 8:22
ፍጥረት ሁሉ በአንድ ላይ እስከ ዛሬ ድረስ በምጥ ጭንቀት ተይዞ በመቃተት ላይ መኖሩን እናውቃለን።
ወደ ሮም ሰዎች 8:22 ගවේෂණය කරන්න
නිවස
බයිබලය
සැලසුම්
වීඩියෝ