1
የዮሐንስ ወንጌል 6:35
መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)
አማ54
ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፥ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።
Compare
የዮሐንስ ወንጌል 6:35ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
2
የዮሐንስ ወንጌል 6:63
ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይተቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።
የዮሐንስ ወንጌል 6:63ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
3
የዮሐንስ ወንጌል 6:27
ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና።
የዮሐንስ ወንጌል 6:27ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
4
የዮሐንስ ወንጌል 6:40
ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 6:40ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
5
የዮሐንስ ወንጌል 6:29
ኢየሱስ መልሶ፦ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው።
የዮሐንስ ወንጌል 6:29ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
6
የዮሐንስ ወንጌል 6:37
አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፤
የዮሐንስ ወንጌል 6:37ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
7
የዮሐንስ ወንጌል 6:68
ስምዖን ጴጥሮስ፦ ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤
የዮሐንስ ወንጌል 6:68ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
8
የዮሐንስ ወንጌል 6:51
ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
የዮሐንስ ወንጌል 6:51ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
9
የዮሐንስ ወንጌል 6:44
የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 6:44ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
10
የዮሐንስ ወንጌል 6:33
የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና አላቸው።
የዮሐንስ ወንጌል 6:33ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
11
የዮሐንስ ወንጌል 6:48
የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
የዮሐንስ ወንጌል 6:48ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
12
የዮሐንስ ወንጌል 6:11-12
ኢየሱስም እንጀራውን ያዘ፥ አመስግኖም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለተቀመጡት ሰዎች ሰጡአቸው እንዲሁም ከዓሣው በፈለጉት መጠን። ከጠገቡም በኋላ ደቀ መዛሙርቱን፦ አንድ ስንኳ እንዳይጠፋ የተረፈውን ቍርስራሽ አከማቹ አላቸው።
የዮሐንስ ወንጌል 6:11-12ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
13
የዮሐንስ ወንጌል 6:19-20
ሀያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ከቀዘፉ በኋላም፥ ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ ታንኳይቱ ሲቀርብ አይተው ፈሩ። እርሱ ግን፦ እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
የዮሐንስ ወንጌል 6:19-20ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
Home
ਬਾਈਬਲ
Plans
ਵੀਡੀਓ