1
የማቴዎስ ወንጌል 19:26
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ኢየሱስም እነርሱን ተመልክቶ “ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል፤” አላቸው።
ႏွိုင္းယွဥ္
የማቴዎስ ወንጌል 19:26ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
2
የማቴዎስ ወንጌል 19:6
ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።”
የማቴዎስ ወንጌል 19:6ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
3
የማቴዎስ ወንጌል 19:4-5
እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አለ “ፈጣሪ በመጀመሪያ ወንድና ሴት አደረጋቸው፤ አለም ‘ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ፤’ የሚለውን ቃል አላነበባችሁምን?
የማቴዎስ ወንጌል 19:4-5ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
4
የማቴዎስ ወንጌል 19:14
ነገር ግን ኢየሱስ “ሕፃናትን ተዉአቸው፤ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና” አለ፤
የማቴዎስ ወንጌል 19:14ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
5
የማቴዎስ ወንጌል 19:30
ነገር ግን ብዙዎቹ ፊተኞች ኋለኞች፥ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።
የማቴዎስ ወንጌል 19:30ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
6
የማቴዎስ ወንጌል 19:29
ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል፤ የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል።
የማቴዎስ ወንጌል 19:29ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
7
የማቴዎስ ወንጌል 19:21
ኢየሱስም “ፍጹም ልትሆን ብትወድ፥ ሂድና ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፤ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፤ መጥተህም ተከተለኝ፤” አለው።
የማቴዎስ ወንጌል 19:21ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
8
የማቴዎስ ወንጌል 19:17
እርሱም “ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ፤” አለው።
የማቴዎስ ወንጌል 19:17ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
9
የማቴዎስ ወንጌል 19:24
ዳግመኛም እላችኋለሁ፤ ባለጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል፤” አለ።
የማቴዎስ ወንጌል 19:24ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
10
የማቴዎስ ወንጌል 19:9
እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፤ የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል፤” አላቸው።
የማቴዎስ ወንጌል 19:9ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
11
የማቴዎስ ወንጌል 19:23
ኢየሱስም ለደቀ መዛሙርቱ “እውነት እላችኋለሁ፥ ለባለጠጋ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት ጭንቅ ነው።
የማቴዎስ ወንጌል 19:23ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
ပင္မစာမ်က္ႏွာ
သမၼာက်မ္းစာ
အစီအစဥ္မ်ား
ဗီဒီယိုမ်ား