1
ኦሪት ዘፍጥረት 22:14
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
አብርሃምም ዛሬ በዚህ ተራራ እግዚአብሔር ፈጽሞ ታየኝ ሲል ያን ቦታ “ራእየ እግዚአብሔር” ብሎ ጠራው።
ႏွိုင္းယွဥ္
ኦሪት ዘፍጥረት 22:14ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
2
ኦሪት ዘፍጥረት 22:2
“የምትወድደውን አንድ ልጅህን ይስሐቅን ይዘህ ወደ ከፍተኛው ተራራ ሂድ፤ እኔም በምነግርህ በአንድ ተራራ ላይ በዚያ መሥዋዕት አድርገህ ሠዋው” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 22:2ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
3
ኦሪት ዘፍጥረት 22:12
እርሱም፥ “በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፤ አንዳችም አታድርግበት፤ ለምትውድደው ልጅህ ከእኔ አልራራህለትምና አንተ እግዚአብሔርን የምትፈራ እንደሆንህ አሁን ዐውቄአለሁ” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 22:12ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
4
ኦሪት ዘፍጥረት 22:8
አብርሃምም፥ “ልጄ ሆይ፥ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል” አለው፤ ሁለቱም አብረው ሄዱ።
ኦሪት ዘፍጥረት 22:8ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
5
ኦሪት ዘፍጥረት 22:17-18
ዘርህንም እንደ ሰማይ ከዋክብትና በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ፈጽሞ አበዛዋለሁ፤ ዘርህም የጠላት ሀገሮችን ይወርሳሉ፤ የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ፤ ቃሌን ሰምተሃልና።”
ኦሪት ዘፍጥረት 22:17-18ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
6
ኦሪት ዘፍጥረት 22:1
ከእነዚህም ነገሮች በኋላ እንዲህ ሆነ። እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው፤ እንዲህም አለው፥ “አብርሃም! አብርሃም ሆይ፥” እርሱም፥ “እነሆ፥ አለሁ” አለ።
ኦሪት ዘፍጥረት 22:1ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
7
ኦሪት ዘፍጥረት 22:11
የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና፥ “አብርሃም! አብርሃም” አለው፤ እርሱም፥ “እነሆኝ” አለ።
ኦሪት ዘፍጥረት 22:11ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
8
ኦሪት ዘፍጥረት 22:15-16
የእግዚአብሔር መልአክም አብርሃምን ከሰማይ ሁለተኛ ጊዜ ጠራው፤ እንዲህም አለው፦ “እግዚአብሔር በራሴ ማልሁ ይላል፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ ለምትወድደው ልጅህም ከእኔ አልራራህምና መባረክን እባርክሃለሁ፤
ኦሪት ዘፍጥረት 22:15-16ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
9
ኦሪት ዘፍጥረት 22:9
እግዚአብሔር ወዳለውም ወደዚያ ቦታ ደረሱ፤ አብርሃምም በዚያ መሠዊያዉን ሠራ፤ ዕንጨትንም ረበረበ፤ ልጁን ይስሐቅንም አስሮ በመሠዊያዉ በዕንጨቱ ላይ በልቡ አስተኛው።
ኦሪት ዘፍጥረት 22:9ရွာေဖြေလ့လာလိုက္ပါ။
ပင္မစာမ်က္ႏွာ
သမၼာက်မ္းစာ
အစီအစဥ္မ်ား
ဗီဒီယိုမ်ား