1
ኦሪት ዘፍጥረት 15:6
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
አብራም በእግዚአብሔር አመነ፤ እምነቱም ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት።
താരതമ്യം
ኦሪት ዘፍጥረት 15:6 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
2
ኦሪት ዘፍጥረት 15:1
ከዚህ በኋላ አብራም ራእይ አየ፤ እግዚአብሔርም “አብራም፥ አትፍራ፤ እንደ ጋሻ ሆኜ ከአደጋ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፤ ታላቅ በረከትም እሰጥሃለሁ” ሲል ሰማው።
ኦሪት ዘፍጥረት 15:1 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
3
ኦሪት ዘፍጥረት 15:5
ቀጥሎም እግዚአብሔር አብራምን ወደ ውጪ አወጣውና “ወደ ሰማይ ተመልከት፤ ከዋክብትን መቊጠር ትችል እንደሆን ሞክር፤ እንግዲህ የአንተም ዘሮች እንደዚህ ይበዛሉ” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 15:5 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
4
ኦሪት ዘፍጥረት 15:4
ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር ቃል “ይህ ኤሊዔዘር የተባለው አገልጋይ የአንተን ሀብት አይወርስም፤ ከአንተ የሚወለደው ልጅ ወራሽህ ይሆናል” ብሎ ሲነግረው ሰማ።
ኦሪት ዘፍጥረት 15:4 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
5
ኦሪት ዘፍጥረት 15:13
እግዚአብሔር አብራምን እንዲህ አለው፦ “የልጅ ልጆችህ በባዕድ አገር ስደተኞች እንደሚሆኑ ዕወቅ፤ እዚያም በባርነትና በጭቈና ለአራት መቶ ዓመት ያስጨንቁአቸዋል፤
ኦሪት ዘፍጥረት 15:13 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
6
ኦሪት ዘፍጥረት 15:2
አብራምም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ጌታ አምላክ ሆይ፥ ምንም ልጅ ስለሌለኝ የምትሰጠኝ በረከት ምን ያደርግልኛል? ሀብቴን የሚወርሰው የደማስቆ ሰው የሆነው ኤሊዔዘር ነው።
ኦሪት ዘፍጥረት 15:2 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
7
ኦሪት ዘፍጥረት 15:18
በዚያን ዕለት እግዚአብሔር ለአብራም እንዲህ በማለት ቃል ኪዳን ገባለት፦ “ከግብጽ ወንዝ ጀምሮ እስከ ኤፍራጥስ ወንዝ ድረስ ያለውን ምድር ሁሉ ለዘሮችህ እሰጣለሁ፤
ኦሪት ዘፍጥረት 15:18 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
8
ኦሪት ዘፍጥረት 15:16
የልጅ ልጆችህ ወደዚህ ተመልሰው የሚመጡት በአራተኛው ትውልድ ነው፤ እስከዚያ የሚቈዩበትም ምክንያት የአሞራውያን ኃጢአት ገና ስላልተፈጸመ ነው።”
ኦሪት ዘፍጥረት 15:16 പര്യവേക്ഷണം ചെയ്യുക
ആദ്യത്തെ സ്ക്രീൻ
വേദപുസ്തകം
പദ്ധതികൾ
വീഡിയോകൾ