1
የዮሐንስ ወንጌል 19:30
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ጌታችን ኢየሱስም ሆምጣጤውን ቀምሶ፥ “ሁሉ ተፈጸመ” አለ፤ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን ሰጠ።
비교
የዮሐንስ ወንጌል 19:30 살펴보기
2
የዮሐንስ ወንጌል 19:28
ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ሁሉ እንደ ተፈጸመ ባየ ጊዜ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ “ተጠማሁ” አለ።
የዮሐንስ ወንጌል 19:28 살펴보기
3
የዮሐንስ ወንጌል 19:26-27
ጌታችን ኢየሱስም እናቱንና የሚወደውን ደቀ መዝሙሩን ቆመው ባያቸው ጊዜ እናቱን፥ “አንች ሆይ፥ እነሆ፥ ልጅሽ” አላት። ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩን፥ “እናትህ እነኋት” አለው፤ ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ተቀብሎ ወደ ቤቱ ወሰዳት።
የዮሐንስ ወንጌል 19:26-27 살펴보기
4
የዮሐንስ ወንጌል 19:33-34
ወደ ጌታችን ኢየሱስም ሄደው ፈጽሞ እንደ ሞተ ባዩ ጊዜ ጭኑን አልሰበሩም። ነገር ግን ከጭፍሮቹ አንዱ የቀኝ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ያንጊዜም ከእርሱ ደምና ውኃ ወጣ።
የዮሐንስ ወንጌል 19:33-34 살펴보기
5
የዮሐንስ ወንጌል 19:36-37
ይህ ሁሉ የሆነው “ከእርሱ ዐፅሙን አትስበሩ” ያለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ሌላዉም መጽሐፍ ደግሞ“ የወጉትን ያዩታል” ይላል።
የዮሐንስ ወንጌል 19:36-37 살펴보기
6
የዮሐንስ ወንጌል 19:17
መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው ቀራንዮ ወደሚባል ቦታ ወጣ።
የዮሐንስ ወንጌል 19:17 살펴보기
7
የዮሐንስ ወንጌል 19:2
ጭፍሮችም የእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ ደፉበት፤ የቀይ ሐር መጐናጸፊያም አለበሱት።
የዮሐንስ ወንጌል 19:2 살펴보기
홈
성경
묵상
동영상