1
ኦሪት ዘፍጥረት 50:20
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
እናንተ ክፋ ነገርን አሰባችሁብኝ፥ እግዚአብሔር ግን ዛሬ እንደ ሆነው ብዙ ሕዝብ እንዲድን ለማድረግ ለመልካም አሰበው።
비교
ኦሪት ዘፍጥረት 50:20 살펴보기
2
ኦሪት ዘፍጥረት 50:19
ዮሴፍም አላቸው፦ “አይዞአችሁ አትፍሩ፤ እኔ በእግዚአብሔር ምትክ የምሆን ነኝ?
ኦሪት ዘፍጥረት 50:19 살펴보기
3
ኦሪት ዘፍጥረት 50:21
አሁንም አትፍሩ፥ እኔ እናንተንና ልጆቻችሁን እመግባችኋለሁ።” አጽናናቸውም ደስ አሰኛቸውም።
ኦሪት ዘፍጥረት 50:21 살펴보기
4
ኦሪት ዘፍጥረት 50:17
ዮሴፍን እንዲህ በሉት፦ ‘እባክህ የወንድሞችህን በደል ኃጢአታቸውንም ይቅር በል፥ እነርሱ በአንተ ከፍተውብሃልና፥ አሁንም እባክህ የአባትህ አምላክ ባርያዎች የበደሉህን ይቅር በል።’”
ኦሪት ዘፍጥረት 50:17 살펴보기
5
ኦሪት ዘፍጥረት 50:24
ዮሴፍም ወንድሞቹን፦ “እኔ እሞታለሁ፥ እግዚአብሔርም መጎብኘትን ይጎበኛችኋል፥ ከዚህችም ምድር ያወጣችኋል፥ ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም ወደ ማለላቸው ምድር ያደርሳችኋል” አላቸው።
ኦሪት ዘፍጥረት 50:24 살펴보기
6
ኦሪት ዘፍጥረት 50:25
ዮሴፍም የእስራኤልን ልጆች፦ “እግዚአብሔር ሲያስባችሁ አጥንቴን ከዚህ አንሥታችሁ ከእናንተ ጋር ውሰዱ ብሎ” አስማላቸው።
ኦሪት ዘፍጥረት 50:25 살펴보기
7
ኦሪት ዘፍጥረት 50:26
ዮሴፍም ዕድሜው መቶ ዐሥር ዓመት ሲሞላው ሞተ፤ በሽቶም አሹት፥ በግብጽ ምድር በሣጥን ውስጥ አኖሩት።
ኦሪት ዘፍጥረት 50:26 살펴보기
홈
성경
묵상
동영상