1
ወደ ሮም ሰዎች 2:3-4
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
አንተ ሰው! እንዲህ በሚያደርጉት ሰዎች ላይ እየፈረድክ፥ እነርሱ የሚያደርጉትን ስታደርግ ከእግዚአብሔር ፍርድ የምታመልጥ ይመስልሃልን? ወይስ የእግዚአብሔርን የደግነቱንና የቻይነቱን፥ የታጋሽነቱንም ብዛት ትንቃለህን? እግዚአብሔር ደግነቱን ያበዛልህ አንተን ወደ ንስሓ ለመምራት እንደ ሆነ አታውቅምን?
Lee anya n'etiti ihe abụọ
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:3-4
2
ወደ ሮም ሰዎች 2:1
በሌላው ሰው ላይ የምትፈርድ አንተ ለራስህ የምታመካኘው የለህም፤ በሌላው ሰው ላይ ስትፈርድ በራስህ ላይ ትፈርዳለህ፤ አንተ በሰው ላይ እየፈረድክ፥ ያ የፈረድክበት ሰው የሚያደርገውን ታደርጋለህ።
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:1
3
ወደ ሮም ሰዎች 2:11
እግዚአብሔር በሰዎች መካከል አያዳላም።
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:11
4
ወደ ሮም ሰዎች 2:13
በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁ ሕጉን ሰምተው በሥራ ላይ የሚያውሉት ናቸው እንጂ ሕጉን ሰምተው በሥራ ላይ የማያውሉት አይደሉም።
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:13
5
ወደ ሮም ሰዎች 2:6
እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ እንደየሥራው ይሰጠዋል።
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:6
6
ወደ ሮም ሰዎች 2:8
የራሳቸውን ጥቅም በሚፈልጉ፥ ለእውነት በማይታዘዙና ለዐመፅ በሚታዘዙ ዐድመኞች ላይ ግን የእግዚአብሔር ቊጣና መቅሠፍት ይመጣባቸዋል።
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:8
7
ወደ ሮም ሰዎች 2:5
እንግዲህ አንተ ንስሓ ባለመግባትህና እልኸኛ በመሆንህ የእግዚአብሔር ቊጣና ትክክለኛ ፍርድ በሚገለጥበት ቀን ቅጣትህ እንዲበዛ ታደርጋለህ።
Nyochaa ወደ ሮም ሰዎች 2:5
Ebe Mmepe Nke Mbụ Nke Ngwá
Akwụkwọ Nsọ
Atụmatụ Ihe Ogụgụ Gasị
Vidiyo Gasị