1
ኦሪት ዘፍጥረት 37:5
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ዮሴፍም ሕልምን አለመ፤ ለወንድሞቹም ነገራቸው።
Compare
ኦሪት ዘፍጥረት 37:5 ખોજ કરો
2
ኦሪት ዘፍጥረት 37:3
ያዕቆብም ዮሴፍን ከልጆቹ ሁሉ ይልቅ ይወድደው ነበር፤ እርሱ በሽምግልናው የወለደው ነበርና። በብዙ ኅብር ያጌጠችም ቀሚስ አደረገለት።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:3 ખોજ કરો
3
ኦሪት ዘፍጥረት 37:4
ወንድሞቹም አባታቸው ከልጆቹ ሁሉ ይልቅ እንደሚወድደው በአዩ ጊዜ ጠሉት፤ በሰላም ይናገሩትም ዘንድ አልቻሉም።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:4 ખોજ કરો
4
ኦሪት ዘፍጥረት 37:9
ደግሞም ሌላ ሕልምን አየ፤ ለአባቱና ለወንድሞቹም ነገራቸው፤ እንዲህም አለ፥ “እነሆ፥ ደግሞ ሌላ ሕልም አለምሁ፤ ሕልሙም እንዲህ ነው፦ ፀሐይና ጨረቃ ዐሥራ አንድ ከዋክብትም ይሰግዱልኝ ነበር።”
ኦሪት ዘፍጥረት 37:9 ખોજ કરો
5
ኦሪት ዘፍጥረት 37:11
ወንድሞቹም ቀኑበት፤ አባቱ ግን ይህን ነገር በልቡ ይጠብቀው ነበር።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:11 ખોજ કરો
6
ኦሪት ዘፍጥረት 37:6-7
እርሱም አላቸው፥ “እኔ ያለምሁትን ሕልም ስሙ፤ እነሆ፥ እኛ በእርሻ መካከል ነዶ ስናስር ነበርና፥ እነሆ፥ የእኔ ነዶ ቀጥ ብላ ቆመች፤ የእናንተም ነዶዎች በዙርያ ከብበው እነሆ፥ ለእኔ ነዶ ሰገዱ።”
ኦሪት ዘፍጥረት 37:6-7 ખોજ કરો
7
ኦሪት ዘፍጥረት 37:20
ኑ፥ እንግደለውና በአንድ ጕድጓድ ውስጥ እንጣለው፤ ክፉ አውሬም በላው እንላለን፤ ሕልሞቹም ምን እንደሚሆኑ እናያለን።”
ኦሪት ዘፍጥረት 37:20 ખોજ કરો
8
ኦሪት ዘፍጥረት 37:28
እነዚያ ይስማኤላውያን ነጋዴዎችም ሲያልፉ ወንድሞቹ ዮሴፍን ከጕድጓድ ጐትተው አወጡት፤ ለይስማኤላውያንም ዮሴፍን በሃያ ብር ሸጡት፤ እነርሱም ዮሴፍን ወደ ግብፅ ወሰዱት።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:28 ખોજ કરો
9
ኦሪት ዘፍጥረት 37:19
አንዱም ለአንዱ እንዲህ አለው፥ “ያ ባለ ሕልም ይኸው መጣ።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:19 ખોજ કરો
10
ኦሪት ዘፍጥረት 37:18
እነርሱም ወደ እነርሱ ሳይቀርብ ከሩቅ አስቀድመው አዩት፥ ይገድሉትም ዘንድ በእርሱ ላይ ተማከሩ።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:18 ખોજ કરો
11
ኦሪት ዘፍጥረት 37:22
ሮቤልም፥ “ደም አታፍስሱ፤ በዚች ምድረ በዳ ባለችው ጕድጓድ ጣሉት፤ ነገር ግን እጃችሁን አትጣሉበት” አላቸው። ሮቤልም እንዲህ ማለቱ ከእጃቸው ሊያድነውና ወደ አባቱ ሊመልሰው ነው።
ኦሪት ዘፍጥረት 37:22 ખોજ કરો
હોમ
બાઇબલ
યોજનાઓ
વિડિઓઝ