1
ኦሪት ዘፍጥረት 32:28
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
ሰውየውም፦ “ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ ያዕቆብ አይባልም፤ ነገር ግን ከእግዚአብሔር ከሰውም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና እስራኤል ይባላል” አለው።
Compare
ኦሪት ዘፍጥረት 32:28 ખોજ કરો
2
ኦሪት ዘፍጥረት 32:26
ከዚያ ሰውየው፦ “የንጋት ጎህ ሊቀድ ነውና ልቀቀኝ” አለው። እርሱም፦ “ካልባረክኸኝ አልለቅህም” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:26 ખોજ કરો
3
ኦሪት ዘፍጥረት 32:24
ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፥ አንድ ሰውም እስከ ንጋት ድረስ ሲታገለው አደረ።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:24 ખોજ કરો
4
ኦሪት ዘፍጥረት 32:30
ስለዚህ ያዕቆብ፦ “እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሆኖም ሕይወቴ ተርፋለች” ሲል የዚያን ቦታ ስም “ጵኒኤል” ብሎ ጠራው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:30 ખોજ કરો
5
ኦሪት ዘፍጥረት 32:25
ያ ሰው ያዕቆብን እንዳላሸነፈውም ባየ ጊዜ፥ የጭኑን ሹልዳ ነካው፥ ያዕቆብም ሲታገለው የጭኑ ሹልዳ ከመገጣጠሚያው ላይ ተለያየ፤።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:25 ખોજ કરો
6
ኦሪት ዘፍጥረት 32:27
ሰውየውም፦ “ስምህ ማን ነው?” አለው። እርሱም፦ “ያዕቆብ ነኝ” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:27 ખોજ કરો
7
ኦሪት ዘፍጥረት 32:29
ያዕቆብም፦ “ልለምንህ፥ ስምህን ንገረኝ” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፦ “ስሜን ለምን ትጠይቃለህ?” አለው። በዚያም ስፍራ ባረከው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:29 ખોજ કરો
8
ኦሪት ዘፍጥረት 32:10
ለባርያህ ካሳየኸው ከጽኑ ፍቅርና ከታማኝነትህ ሁሉ ትንሽ ስንኳ የማይገባኝ ነኝ፥ በትሬን ብቻ ይዤ ይህን ዮርዳኖስን ተሻግሬ ነበር፥ አሁን ግን ለሁለት ወገን የተከፈልኩ ሆንሁ።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:10 ખોજ કરો
9
ኦሪት ዘፍጥረት 32:32
ስለዚህም የያዕቆብን ጭን ይዞ የወርቹን ሹልዳ ነክቶታልና፥ የእስራኤል ልጆች እስከ ዛሬ ድረስ የወርችን (በጭን መጋጠሚያ ላይ ያለውን) ሹልዳ አይበሉም።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:32 ખોજ કરો
10
ኦሪት ዘፍጥረት 32:9
ያዕቆብም አለ፦ “የአባቴ የአብርሃም አምላክ ሆይ፥ የአባቴም የይስሐቅ አምላክ ሆይ፥ ‘ወደ ትውልድ አገርህ ወደ ተወለድህበትም ስፍራ ተመለስ፥ በጎነትንም አደርግልሃለሁ’ ያልኸኝ ጌታ ሆይ፥
ኦሪት ዘፍጥረት 32:9 ખોજ કરો
11
ኦሪት ዘፍጥረት 32:11
ከወንድሜ ከዔሳው እጅ አድነኝ፥ መጥቶ እንዳያጠፋኝ፥ እናቶችንም ከልጆች ጋር እንዳያጠፋ እኔ እፈራዋለሁና።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:11 ખોજ કરો
હોમ
બાઇબલ
યોજનાઓ
વિડિઓઝ