1
ኦሪት ዘፀአት 20:2-3
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
“ከግብጽ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁህ ጌታ አምላክህ እኔ ነኝ። “ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይኑሩህ።
Comparer
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:2-3
2
ኦሪት ዘፀአት 20:4-5
በላይ በሰማያት ካለው፥ በታች በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም አምሳል፥ የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ። አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውም፤ እኔ ጌታ አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና በሚጠሉኝ እስከ ሦስተኛና እስከ አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ፥
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:4-5
3
ኦሪት ዘፀአት 20:12
“ጌታ አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም፥ አባትህንና እናትህን አክብር።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:12
4
ኦሪት ዘፀአት 20:8
“እንድትቀድሰው የሰንበትን ቀን አስታውስ።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:8
5
ኦሪት ዘፀአት 20:7
“የጌታ የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ ጌታ ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ሳይቀጣው አያልፍም።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:7
6
ኦሪት ዘፀአት 20:9-10
ስድስት ቀን ሥራህን ሥራ፥ ተግባርህንም ሁሉ ፈጽም፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለጌታ አምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህ፥ ሴት ልጅህ፥ ወንድ ሠራተኛህ፥ ሴት ሠራተኛህ፥ ከብትህ፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ መጻተኛ ሁሉ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:9-10
7
ኦሪት ዘፀአት 20:17
“የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፤ የባልንጀራህን ሚስት፥ ወንድ ሠራተኛውን፥ ሴት ሠራተኛውን፥ በሬውን፥ አህያውን፥ የባልንጀራህ የሆነውን ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ።”
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:17
8
ኦሪት ዘፀአት 20:16
“በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:16
9
ኦሪት ዘፀአት 20:14
“አታመንዝር።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:14
10
ኦሪት ዘፀአት 20:13
“አትግደል።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:13
11
ኦሪት ዘፀአት 20:15
“አትስረቅ።
Explorer ኦሪት ዘፀአት 20:15
Accueil
Bible
Plans
Vidéos