መጽሐፈ መዝሙር 123
123
ምሕረት ለማግኘት የቀረበ ጸሎት
1እግዚአብሔር ሆይ! ዙፋንህ በሰማይ ወደ ሆነው
ወደ አንተ እመለከታለሁ።
2እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ!
አገልጋዮችና ገረዶች የአሳዳሪዎቻቸውን እጅ እንደሚጠባበቁ ሁሉ
እኛም እስክትምረን ድረስ የአንተን ምሕረት
ለማግኘት እንጠባበቃለን።
3እግዚአብሔር ሆይ! ብዙ ስድብ ስለ ደረሰብን ማረን!
እባክህ ማረን!
4በትዕቢተኞች ብዙ መዋረድ፥
በትምክሕተኞችም ብዙ መናቅ ደርሶብናል።
Currently Selected:
መጽሐፈ መዝሙር 123: አማ05
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997