YouVersion Logo
Search Icon

መጽሐፈ መዝሙር 123

123
ምሕረት ለማግኘት የቀረበ ጸሎት
1እግዚአብሔር ሆይ! ዙፋንህ በሰማይ ወደ ሆነው
ወደ አንተ እመለከታለሁ።
2እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ!
አገልጋዮችና ገረዶች የአሳዳሪዎቻቸውን እጅ እንደሚጠባበቁ ሁሉ
እኛም እስክትምረን ድረስ የአንተን ምሕረት
ለማግኘት እንጠባበቃለን።
3እግዚአብሔር ሆይ! ብዙ ስድብ ስለ ደረሰብን ማረን!
እባክህ ማረን!
4በትዕቢተኞች ብዙ መዋረድ፥
በትምክሕተኞችም ብዙ መናቅ ደርሶብናል።

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in