መዝሙረ ዳዊት 9:1-10
መዝሙረ ዳዊት 9:1-10 አማ2000
አቤቱ፥ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፥ ታምራትህንም ሁሉ እናገራለሁ። በአንተ ደስ ይለኛል፥ ሐሤትንም አደርጋለሁ፤ ልዑል ሆይ፥ ለስምህ እዘምራለሁ። ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው በተመለሱ ጊዜ፥ ይታመሙ፥ ከፊትህም ይጥፉ። ፍርዴንና በቀሌን አድርገህልኛልና፤ የጽድቅ ፈራጅ ሆይ፥ በዙፋንህ ላይ ተቀመጥህ። አሕዛብን ገሠጽህ፥ ዝንጉዎችም ጠፉ፥ ስማቸውንም ለዘለዓለም ደመሰስህ። ጠላቶች በጦር ለዘለዓለም ጠፉ፥ ከተሞቻቸውንም አፈረስህ፥ ዝክራቸውንም በአንድነት ታጠፋለህ። እግዚአብሔር ግን ለዘለዓለም ይኖራል፥ ዙፋኑንም ለመፍረድ አዘጋጀ፤ እርሱም ዓለምን በጽድቅ ይዳኛታል። አሕዛብንም በቅንነት ይዳኛቸዋል። እግዚአብሔርም ለድሆች መጠጊያ ሆናቸው፥ እርሱም በመከራቸው ጊዜ ረዳታቸው ነው። ስምህን የሚወዱ ሁሉ በአንተ ይታመናሉ፥ አቤቱ፥ የሚሹህን አትተዋቸውምና።




