1
ምሳሌ 4:23
አዲሱ መደበኛ ትርጒም
NASV
ከሁሉም በላይ ልብህን ጠብቅ፤ የሕይወት ምንጭ ነውና።
አወዳድር
{{ጥቅስ}} ያስሱ
2
ምሳሌ 4:26
የእግርህን ጐዳና አስተካክል፤ የጸናውን መንገድ ብቻ ያዝ።
3
ምሳሌ 4:24
ጥመትን ከአፍህ አስወግድ፤ ብልሹ ንግግርም ከከንፈሮችህ ይራቅ።
4
ምሳሌ 4:7
ጥበብ ታላቅ ነገር ናት፤ ስለዚህ ጥበብን አግኛት፤ ያለህን ሁሉ ብታስከፍልህም ማስተዋልን ገንዘብህ አድርጋት።
5
ምሳሌ 4:18-19
የጻድቃን መንገድ ሙሉ ቀን እስኪሆን ድረስ፣ ብርሃኑ እየጐላ እንደሚሄድ የማለዳ ውጋጋን ነው። የክፉዎች መንገድ ግን እንደ ድቅድቅ ጨለማ ነው፤ ምን እንደሚያሰናክላቸውም አያውቁም።
6
ምሳሌ 4:6
ጥበብን አትተዋት፤ እርሷም ከለላ ትሆንሃለች፤ አፍቅራት፤ እርሷም ትጠብቅሃለች።
7
ምሳሌ 4:13
ምክርን አጥብቀህ ያዛት፤ አትልቀቃት፤ ጠብቃት፤ ሕይወትህ ናትና።
8
ምሳሌ 4:14
ወደ ኃጥኣን ጐዳና እግርህን አታንሣ፤ በክፉ ሰዎች መንገድ አትሂድ፤
9
ምሳሌ 4:1
ልጆቼ ሆይ፤ የአባትን ምክር አድምጡ፤ ልብ ብላችሁ ስሙ፤ ማስተዋልንም ገንዘብ አድርጉ።
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች